የኤማሁስ መንገድ

መጽሔቷን ለማግኘት ይህን ይጫኑ

. . . የዘመናችን ተዋሥኦ በይዘቱም ሆነ በመንገዶቹ በግልብነት በእጅጉ የተጠቃ ነው ። ‘በይዘቱ እንዴት ?’ቢባል ሁነቶች ላይ ያተኮረ እና ወቅታዊነትን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ ። አንድም አቋም ከመያዝና ጎራ ከፍሎ ከመናቆር ባለፈ የእውነት የመማር እና የማሰላሰል ጉጉት የማይታይበት በመሆኑ ። በዚህ ተዋሥኦ ውስጥ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ማንሣት እና ከሁነቶቹ የሚሻገር እና ሐሳባዊ የሆነ ትንተና ለማካሔድ መሞከር ትኩረት ያስነሣል ፤ ሲብስም አጉል እንደመራቀቅ ይታያል ።

የሚካሄድበት ከባቢ እና ዘመን ደግሞ ሌላ ግልብነት ደርቦለታል ። በእኛ ሀገር ብቻ ሳይሆን በሌሎችም ሀገራት ፣ ከዘመናዊነትና ከቴክኖሎጂ መራቀቅ ጋር ተያይዞ ሕዝባዊ ተዋሥኦ በጠቅላላው ስለቱን እና ርቀቱን እንዲያጣ ሆኗል ። የሚነበብም ሆነ የሚታይ ወይም የሚደመጥ ነገር አጭር መሆን አለበት ። ነገር ግን ጠቃሚና ወሳኝ ርእሶች እንዲህ ባለ መንገድ ሊስተናገዱ አይችሉም ። የሚያጠግብ ፍሬ ከሌለበት የተመልካቹ እና የአንባቢው ብዛት ምን ጥቅም ይኖረዋል ?

እንዲህ ባለው ከባቢ ውስጥ ሁነቶችን ከሁነትነታቸው እና ከሚያመጡት ወቅታዊ ውጤት በተሻገረ መልኩ ለመመልከት እንቸገራለን ። ቀድሞውኑም (እይታችን ከመጥበቡ የተነሣ) ጠባብ አድርገን የቀረጽነውን አጀንዳ በምንገልጽበት መንገድ የበለጠ እናጠብበዋለን ።

ነገር ግን ሁነቶችን እና ሒደቶችን ከመሠረታቸው መመርመራችን እና የምናቀርባቸው መፍትሔዎችም እንዲሁ የማይናወጥ መሠረት ያላቸው መሆናቸው አስፈላጊ ከሆነ ተዋሥኦውም እንዲሁ የጠለቀ እና የረቀቀ መሆን አለበት ። ይህን ለማድረግ ደግሞ ጊዜ ወስዶ ማሰብ ፣ ማንበብ ፣ ማጠናቀር ፣ መወያየት ፣ መሟገት እና እንዲህ ካለው ሒደት የሚወጡትን ሐሳቦች የሚገባውን ጊዜ ወስዶ መጻፍ እና መናገር የግድ ነው ።

በተለይ የጽሑፎች አስፈላጊነት ደግሞ የተለየ ነው ። ጽሑፍ ከሌሎች ሐሳብን ማቅረቢያ አማራጮች ይልቅ ንጥር የሆኑ ሐሳቦች የሚገኙበት መንገድ ነው ። ጸሐፊው ሐሳቡን ለመግለጽ በአንድ ጊዜና ቦታ ሳይወሰን ፣ ደጋግሞ አስቦ ፣ ደጋግሞ ሞክሮ እስኪዋጣለት እና በበቂ መጠን ለማለት የፈለግሁትን ገልጫለሁ ብሎ እስኪያስብ ድረስ ሐሳቡን የሚያጠራበትን ዕድል የሚሰጥ ጎዳና ነው ። በመሆኑም መፍጠር ለምናልመው ተዋሥኦ ጽሑፍ የማይተካ ሚና አለው ። ያለ ጸሑፍ የሐሳቦች የማደግ አቅም የተወሰነ ነው ።

እንዲህ ያለውን ጽሑፋዊ ተዋሥኦ ለማድረግ ደግሞ እንዲህ ላሉ ጽሑፎች የተዘጋጀ መድረክ መኖር አለበት ። አሁን ያለው ከባቢ ግን ጽሑፍን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘነጋ እና እያገለለ ያለ ነው ። እንዲህ ያለው ጥልቅ እና ሰፊ ተዋሥኦ ቀርቶ ፥ ቀድሞ የነበረው ከወቅታዊ ጉዳዮች ያልዘለለ የጋዜጣ እና የመጽሔት ተዋሥኦ እንኳን ወደ መሞት ቀርቧል ።

ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ወዳለው ሁኔታ ስንመጣ ደግሞ ፥ እንዲህ ያለ ደንበኛ ተዋሥኦ ካለመኖሩም በላይ ፥ አሉ የሚባሉትም ምእመናንን ያገለሉ እና ዘመኑ ካመጣቸው ማዕበሎች ጨርሶ የተፋቱ ናቸው ። ራሳቸውን ካገኙበት ቦታ በግትርነት ወደፊት ከመግፋት ባሻገር ፥ መሠረታዊ የሆኑ ጉዳዮችን ላለማንሣት እና የቆሙበትን ቦታ ተገቢነት ላለመፈተሽ የቆረጡ ናቸው ።

በመሆኑም እንዲህ ያለው የጽሑፍ ተዋሥኦ የሚጠነሰስበት እና የሚዳብርበት ፣ ክርስትናን መሠረት ያደረገ መድረክ እንደሚያስፈልግ በማመን ፥ ኤማሁስ ፕሬስ ፥ ይህቺን ኤማሁስ የተሰኘች ፥ በጊዜያዊነት በኤሌክትሮኒክ ሚዲያ ፣ ወደፊት ግን በሕትመትም ጭምር ፥ በየሦስት ወሩ ለሕዝብ የምትደርስ መጽሔት ይዞ መጥቷል ።

፠ ፠ ፠

ኤማሁስ ‘መጽሔት’ ብትሰኝም ቅሉ ይዘቷ ለአካዳሚያዊ ጽሑፎች የሚቀርብ ይሆናል ። ከኤማሁስ ጀርባ ያለው ሐሳብ በትምህርቱ ዓለም (ቢያንስ በፊት) እንደሚደረገው ጥልቀት ያላቸው ጽሑፎችን ማስተናገድ ሲሆን ነገር ግን አሁን እየሆነ እንዳለው ከሕዝባዊው ተዋሥኦ ያልተነጠለ ፣ ይልቁንም በአንባቢነትም ሆነ በጸሐፊነት ለመሳተፍ ለሕዝቡ ክፍት የሆነ ተዋሥኦ መፍጠር ነው ። በመሆኑም ኤማሁስ ከተለመዱት መጽሔቶች በተለየ መልኩ ከሁነቶች ይልቅ መሠረታዊ ሐሳቦች ላይ ያተኮሩ ፥ ወቅታዊ ጉዳዮችን ያማከሉ ነገር ግን ፍልስፍናዊ ይዘት እና ውቅር ያላቸውን ጽሑፎች ታስተናግዳለች ። የጸሐፊውን ስሜቶች እና አስተያየቶች መገለጻቸውን የምትወድ ፥ ነገር ግን ምክንያታዊነት ያልተለያቸው እንዲሁም የፍልስፍና እና የሐቅ መሠረት ላይ የቆሙ መሆናቸውን የምትጠይቅ ፥ ይህም መሆኑ እንዲታወቅ እንደ ትምህርታዊ ጽሑፎች በማጣቀሻዎች መደገፋቸውን የምታስገድድ ፣ ጠባብ በሆኑ የገጽ ብዛት ክልከላዎች ሐሳቦች እንዳይገደቡ ሰፊ ነፃነት የምትሰጥ መድረክ ትሆናለች ።

ከዚህ ይዘቷ እና ውቅሯ የተነሣም ወደ ሕዝብ ለመድረስ ሦስት ወር ያህል በዝግጅት ትቆያለች ። የሚነሡትን ሐሳቦች ስፋትና ጥልቀት ለማስተናገድ ስትል ሆዷን ታሰፋለች ፤ መለስ ያለ መጽሐፍ አክላ ትመጣለች ።

ለዚህ መድረክ የሚመጥኑ ጽሑፎችን ማዘጋጀት በእጅጉ አድካሚ ከመሆኑ የተነሣ ቢያንስ እስከ ጊዜው ድረስ የኤማሁስ አባላት በዋናነት የጸሐፊነት ሚናን መወጣት ቢኖርባቸውም ፣ ተስፋው ግን ከላይ እንደተባለው መድረኩ ሕዝባዊ እንዲሆን እና ብዙዎች በጸሐፊነት እንዲሳተፉ ነው ። ብዙ ሰዎችን ብቻም ሳይሆን ፥ ብዙ ዓይነት ሐሳቦችንም የሚያሳትፍ ተዋሥኦ መሆን አለበት ። የስምምነት እና የመደጋገፍ ብቻ ሳይሆን የሙግትም መድረክ ነው ለመፍጠር የምናልመው ።

ከአባቶቻችን ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቷን እና ትውፊቷን የጠበቀችው እንዲህ ባለ ክርስቲያኖች እውነትን ፍለጋ በሚሟገቱበትም ተዋሥኦ ጭምር  በመሆኑ እንዲህ ያለው ሙግት ለእኛ ዐዲስ ነገር ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ትውፊት የማስቀጠል ተግባር ነው ። ሌላው ቀርቶ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ያሉ ሰዎች እንኳን ሊሞግቱን ቢወዱ በቀናነት ለማስተናገድ በራችን ክፍት ይሆናል ። የክርስቲያኖች እምነት ባለማወቅ የሚጠበቅ ሳይሆን ተፈትኖ ያለፈ እና የጠራ መሆን አለበት ። አንድም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለነውን ከማጽናት ባለፈ ሌሎችን ወደዚህ ኅብረት መጥራትም የተልዕኮአችን ዋና አካል ስለሆነ ፥ የተዋሥኦውን አድማስ በተቻለ መጠን ማስፋት አስፈላጊ እንደሆነ እናምናለን ። ስለዚህም እንዲህ ያለውን ጥልቅ እና እውነትን መዳረሻው ያደረገ ተዋሥኦ የሚሹትን ሁሉ በማንበብም ፣ በመጻፍም ይሳተፉ ዘንድ እንጋብዛለን ።

እነኋት ኤማሁስ ።

Click to download

Share...

Facebook
Telegram
WhatsApp
X
Email
Print
20 Comments
  • Mule geda
    Mule geda
    August 3, 2025 at 9:02 pm

    ቃለሕይወት ያሰማልን

    Reply
    • Tesfalem
      Tesfalem
      August 4, 2025 at 4:04 pm

      Looking forward to it.

      Reply
      • Dawit
        Dawit
        August 5, 2025 at 3:17 pm

        Thanks so much for everything you have done

        Reply
        • Abenet W.
          Abenet W.
          September 7, 2025 at 10:21 am

          may God bless you and your pen too

          Reply
      • Abriham
        Abriham
        August 10, 2025 at 7:15 am

        እግዚአብሔር አገልግሎታችሁን ይባረክልን :በ podcast ብዙ እያተረፍን ነዉ በዚህ መምጣታችሁ ደግሞ የበለጠ እንድናተርፍ ይረዳናል እና በርቱልን

        Reply
        • Sola@1621
          Sola@1621
          August 15, 2025 at 12:42 pm

          እግዚአብሔር የቅዱሳንን ጥበብ ያድልልን

          Reply
    • Alamaw Zemenu
      Alamaw Zemenu
      August 5, 2025 at 10:19 am

      “ጥሩ ነው በርቱ (ጥልቀት ያላቸው ሀይማኖታዊ ምርምሮችን ጨምራቸሁ ለአንባቢያን ክፍት ብታደርጉ) ።

      Reply
      • Malik Nasir
        Malik Nasir
        August 8, 2025 at 10:11 am

        ከዛሬ ጀምሮ የመጽሔቷ ደንበኝነቴን አረጋግጣለኹ ።

        ቃለ ሕይወት ያሰማልን 🙏

        Reply
      • Bezaalem
        Bezaalem
        August 8, 2025 at 12:12 pm

        በርቱ ጊዜውን መዋጀት ያስፈልጋል።ይበል የሚያሰኝ ጅማሮ ነው።እንደ ቤተ ክርስቲያን ገና ብዙ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች አሉብንና ወደፊት

        Reply
    • demere
      demere
      August 9, 2025 at 6:17 am

      በጣም አሪፍ ነው

      Reply
    • አሸናፊ
      አሸናፊ
      August 14, 2025 at 2:01 pm

      እግዚአብሔር ያበርታቹ፣ የአገልግሎት ዘመናቹ ይባረክ:: ከወቅቱ ከሚመጣውም ጠላት እመብርሃን ትጠብቃቹ:: እንዲ ነው እንጂ ፣ የማንም ጥራዝ ነጠቅ ሁሉ $creen ሲያገኙ ጊዜ መርዝ ይተፋሉ:: በርቱልን:: ከጎናቹ ነን::

      Reply
  • Yordanos Ayelgn
    Yordanos Ayelgn
    August 4, 2025 at 9:00 am

    የአገልግሎት ዘመናችሁን ይባርክላችሁ🙏

    Reply
    • Yohannes Araya
      Yohannes Araya
      August 4, 2025 at 8:34 pm

      ክፍት የሆነ የደጋፊንም የተቃዋሚን ሃሳብ ለመስማት የተዘጋጃቹ ልበ ሰፊ ስለሆናቹ ወደ ፊት ትልቅ ስራ እንደምትሄዱ እርግጠኛ ነኝ💪💪ጌታ በሁሉም ነገር ከናተ ጋር ይሁን🙏🙏

      Reply
  • መ/ር አስቻለው ኮላ፦ከመቂ ከተማ
    መ/ር አስቻለው ኮላ፦ከመቂ ከተማ
    August 4, 2025 at 9:01 am

    እጅግ ደሥ የሚል እይታ ነው። ሙግት የሚለው ትንሽ ከበድ የሚል ቢሆንም ሐይማኖታዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ እና ብዙም እንደምንማር ተሥፋ አደርጋለሁ። እንደቀደምት አበው የዘመኑ የቤተክርስቲያን ልጆቿም ብዙ ይተጋሉ፤ ለቀጣዩም ያስረክባሉ። ኮርቻለሁ፤ በርቱልን!!
    ፈጣሪ አምላክ ይባርካችሁ!!

    Reply
    • surafel
      surafel
      August 4, 2025 at 4:44 pm

      እግዚአብሔር ይስጥልን ጥቅምት ላይ እንገናኝ

      Reply
      • Biniyme
        Biniyme
        August 4, 2025 at 6:37 pm

        አሪፍ ነው

        Reply
      • Nebiyu Tilahun
        Nebiyu Tilahun
        August 13, 2025 at 11:27 am

        እግዚአብሔር ይስጥልን!❤
        በእውነት ድንቅ ነው!❤

        Reply
    • Astaa
      Astaa
      August 5, 2025 at 2:12 am

      ሙግት መኖር አለበት። ጤናማ ሙግት የሌለበት ተዋስኦ ሞዉት ነው። ይህ ዓይነት ባለመኖሩ የቀዘቀዘ፣የተደናበረ ምእመን ተፈጥሯል። በዚህም የተነሳ በቤት ውስጥ ይሁን በውጭ ያሉ እንዲጋልቡት ምቹ ሆኗል። የግላቸው መንጋ መሥራት ለሚፈልጉ ምቹ ገበያ ሆኗል።

      Reply
      • Israel
        Israel
        August 9, 2025 at 9:31 am

        ቃለህይወት ያሰማልን
        አሪፍ ነዉ።

        1.በርቱ ግን Meaninglessness በተመለከተ ያንሳል።Existentialism እና ቡዲዝም በደንብ ቢታይ ?
        2.እንደሚታወቀዉ የቤተሰብ ዉቅር በየቤታችን እንዲፈረስ ተደረጓል ? ካለም በብዙ መለያየቶች ዉስጥ ነዉ “በሃይማኖት” ሳይቀር ይህ የሚያመጣዉ አደጋ በራሱ በጥልቀት ቢቀርብ? ከልጆች አስተዳደግ ጋር ሲያያዝ ደግሞ ሌላ ታሪክ ይህም ቢታይ?

        3.እናዉጋ ላይ አማራነት አና ክርስትና እንኳን Boaring
        ነበር።ለመሆኑ የአፍሪካ ሀገሮች ሁሉ ከኛ Missionary mindset ደካማነት በተነሳ እንዳልከዉም የቅርስ እና ፉከራ ብዛት ዘረኝነት(ለዛዉም በደብር ሁላ)አኛንም እነሱንም እስካሁን ለWestern እና ለIslamic Captivity ተላልፈዉ እንዲሰጡት አላደረግንም ?
        Orthodox is Missionary.ግን ነዉ እኛጋ?ለምን ?
        4.”አበ ነፍስ” በክርስትና ሕይወት ዉስጥስ?

        በርቱ !!!
        ችግሩ የጋራ ነዉ ደሞ ።
        ብሶቴን በአንዴ😂

        Reply
  • Sileshe D. Girma
    Sileshe D. Girma
    August 4, 2025 at 9:14 am

    መልካም መንገድ
    እግዚያብሔር ከከፉ ይጠብቃችሁ።
    ስለምትሰጡን እውቀት ሁሉ
    እጅ ነስቻለሁ።
    በተቻለኝ አዳምጣችኋለሁ።
    ደሞም አነባለሁ።
    በርቱ!!!

    Reply
Leave a Reply to Yohannes Araya Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

Guest Posts
መሐሪ ዘመልአክ

የአእላፋት ዝማሬ ምልክት ነው ።

መግቢያ በዘመናችን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የታየው “የአእላፋት ዝማሬ” የተባለው ክሥተት ሰፊ የሆነ ሕዝባዊና ሊቱርጊያዊ ውይይት አስነስቷል። አንዳንዶች ይህን እንቅስቃሴ እንደ መንፈሳዊ ንቃትና የራቁ ምእመናን ተሳትፎ መመለሻ ሲያቀርቡት፣ ሌሎች ደግሞ ከቤተ ክርስቲያን ትውፊታዊ ሊቱርጊያ[1] ጋር የሚጋጭ እና ሥርዓታዊ መነሻዋን የሚያዳክም ክዋኔ እንደሆነ ይገምግሙታል። ወንድማችን በርናባስ ሽፈራው የጻፈው “የአእላፋት ዝማሬ”ን የተመለከተ የኤማሁስ ገጽ ጽሑፍ አንዳንዶችን ሲያበሳጭ፣ ሌሎችን ሲያሳስብ እንደሰነበተ በአረቦን ቴሌግራም ቻነል ላይ ተመልክቻለኹ። 23 ገጾችን የያዘ፣ ንዑሳን አርእስት በግልጽ ያልተሰጡት ረዥም ጽሑፍ ስለኾነ ጊዜ ሰጥቶ ማንበብን፣ ካነበቡም በኋላ ዐበይት መከራከሪያዎቹን ማጥለልን ይጠይቃል። እንዲኽም ኾኖ፣ ቢያንስ መሠረታዊ የኾነ የሊቱርጊያዊ ነገረ መለኮት (liturgical theology) ንባብ ለሌለው ሰው ጽሑፉ ከንቱ ምቀኝነት፣ መራራነት፣ አማራሪነት፣ ጠብ ያለሽ በዳቦ ሊመስል ይችላል። በዋናነት እየነቀሰ የሚተቸው “የአእላፋት ዝማሬ”ን ልዩ ልዩ መልኮች ይኹን እንጂ፣ መሠረታዊ ጉዳዩ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በአኹኑ ጊዜ ያለችበትን ሊቱርጊያዊ ቀውስ (liturgical crisis) መጠቆም ኾኖ አግኝቼዋለኹ። ጉዳዩ እኔንም ሲያሳስበኝ የነበረ ነገር ስለነበረ የበርናባስን ሐሳብ እንዲኽ ልለጥቀው ወደድኹ። የእኔ ጽሑፍ የ“የአእላፋት ዝማሬ”ን እንደ ምልክት በመመልከት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ የምትገኝበትን ሊቱርጊያዊ ቀውስ ይጠቁማል። በተለይም በቋንቋ ባዕድነት፣ በዜማ ውስብስብነትና በሰዓት ምቹ አለመኾን ምክንያት ምእመናን ከ“ሰዓታት ጸሎት” የራቁበትን ኹኔታና ኮንሰርታዊ ዝግጅቶች በተግባር የተኩት የሊቱርጊያ ባዶ (liturgical vacuum) ምን እንደሆነ ለማመልከትና መፍትሔውን ለማሳየት ይጥራል። The Problem of Reactive Ministry እና Institutional Survivalism በርናባስ በጽሑፉ የሚተቸው አንዱ ነገር ይኽ ተልእኮን

Read More »
Emmaus Posts
በርናባስ ሽፈራው

“የአእላፋት ዝማሬ”

ሁለተኛው የአእላፋት ዝማሬ ባለፈው ዓመት በልደት ዋዜማ ተካሔደ ። በአዘጋጆቹ እና በተሳታፊዎቹ ዘንድ ይህ ሁለተኛው ዙር ከመጀመሪያው ዙር በላይ ያማረ እና የሠመረ ሆኖ ተቆጥሯል ። በጠቅላላው ከምእመናን በኩል በተሳትፎም ሆነ በማኅበራዊ ሚዲያ ያገኘው ተቀባይነት ሌሎች ሁነቶች ሲሆኑ እንደምናየው በጅምር የሚቀር ሳይሆን እንደ ባህል የመተከል ዕድሉ ሰፊ መሆኑን ያመላክታል ። እንዲያውም በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ብቻ ሳይወሰን ወደ ሌሎች ቦታዎችም እንዲሰፋ የሕዝብ ጥያቄ እና በአዘጋጆቹም በኩል እቅድ መኖሩ ይታወቃል ። ስለዚህ በጥቂት ዓመታት ውስጥ ልክ እንደ ጥምቀት ሁሉ በሁሉም ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ (የአዘጋጆቹ አቅም በፈቀደው ልክ) የአእላፋት ዝማሬ የልደት በዓል መለያ ሆኖ እንዲካሔድ መጠበቅ እንችላለን ። ይህ ነገር በብዙዎች ዘንድ ለቤተ ክርስቲያን ታላቅ ጥቅም የሚሰጥ ሆኖ ይታያል ። በእነርሱ ዐይን ይህ ሁነት ቤተ ክርስቲያን በብዙዎች ዘንድ እንድትታወቅ ያደርጋል ። ብዙዎች በዓሉን አስመልክተው ከሚሔዱባቸው የማይገቡ ዓውዶች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲመለሱ ከማድረጉ ባሻገር ፥ በቤተ ክርስቲያን ሱታፌ ያላቸውንም በሚስብ እና በሚገባቸው መልኩ ቤተ ክርስቲያንን የበለጠ እንዲያውቋት ያስችላቸዋል ። ስለዚህም የሌሉትን በመጥራት ፥ ያሉትንም በማጽናት ቤተ ክርስቲያን ዘመኑን እንድትዋጅ የሚያስችላት መሣሪያ ነው ፤ ከእርሷ ዘንድ ወደ ክሕደት እና ወደ ኑፋቄ የፈለሰውን ፥ ወይም በስም ክርስቲያን ሆኖ እና ማዕተብ አስሮ ሳለ በምድራዊ ተድላ ባሕር የሰጠመውን ወጣት ወደ ራሷ የምትስብበት መረብ ነው ። ነገር ግን ከኖረው የቤተ ክርስቲያን ትውፊትና አስተምህሮ አንጻር ከመረመርነው ፥ ይህ ሁነት

Read More »
Emmaus Posts
ኤልያስ ገብረ ሥላሴ

መከራ ፣ እከይ እና ክርስትና

መከራ በክርስቲያኖች ሕይወት ውስጥ ድንገተኛ የሆነ ክስተት አይደለም ። ፍቅር በሆነው እግዚአብሔር ለጥቅማችን የሚፈቀድ የእርምት መንገድ ነው እንጂ ። በየዘመኑ ቤተክርስቲያን በወቅታዊ ሁነቶች እንድትወጠር እና መሠረታዊ ነገሮች ትኩረት እንዳያገኙ የሚቀርብ ፈተና አለ ። ሰበር ዜናዎች ፣ ወቅታዊ አጀንዳዎች ፣ አከራካሪ ጉዳዮች ወዘተ ከመነኩሴ መቁጠሪያ በላይ በሚሽከረከሩበት ዘመን ላይ ነው የምንገኘው ። እነዚህ ሁነቶች ትኩረታችንን ይወስዱትና ሳይታወቀን መሠረታዊ ከሆኑትና ዘለዓለማዊነታችንን ከሚበይኑት ጉዳዮች ወጥተን ምድራዊና እዚሁ ቀሪ በሆኑ ጉዳዮች ተወጥረን እንገኛለን ። እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ሁኔታ በቤተክርስቲያንን መምህራን እና “ተጽዕኖ ፈጣሪዎች” ላይ እጅግ በርትቶ የሚታይ መሆኑ እና በቤተክርስቲያን ዐውደ ምሕረት እና መድረኮች ሳይቀር ሰፊውን ሰዓት መያዙ ነው ። የቤተክርስቲያን ተልእኮ ስለ ክርስቶስ ምስክር መሆን ነው ። መሠረታዊ ካልሆኑት ሁነቶች ወጥተን ወደዚህ ዋነኛ ተልእኮአችን እንድንመለስ ተዋሥኦ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ። ይህ በምእመናን ፥ በተለይ ደግሞ በቤተክርስቲን አገልጋዮች ፥ ዘንድ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ነገር ነው ። የሁነቶችን መሠረት መመርመርና ትክክለኛ ባሕርያቸውን መረዳት ያሻል ። ሁነቶቹ ችግሮች የሆኑ እንደሆነ ሥር ነቀል መፍትሔ ማሰብ የሚቻለው ፥ መልካም አጋጣሚዎችም ከሆኑ በትክክለኛው መንገድ ጥቅም ላይ ልናውላቸው የምንችለው የሁነቶቹን መሠረት በጥልቀት መረዳት ከቻልን ነው ። በመቀጠልም ተከትለው ሊደረጉ ስለሚገቡ ነገሮች መወያየት ከተቻለ ብቻ ነው ። ካልሆነ አሁን እየሆነ እንዳለው የወቅታዊ አጀንዳዎች አሳዳጅ ብቻ ሆነን ነው የምንቀረው ። በተለይ ዘመናችን የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ስለሆነ በዚህ

Read More »
Emmaus Posts
መሐሪ ዘመልአክ

ከእውነት አልባነት ጋር የሚካሔድ ሙግት

(‘ሐሳቦች መዘዝ አላቸው’ በሚል ርእስ በኤማሁስ መጽሔት ቅጽ 1 ፣ ቁጥር 1 በወጣው ጽሑፍ ላይ የተጻፈ አስተያየት) በመሐሪ ዘመልአክ (PhD) ከዛሬ አሥራ አምስት ዓመታት በፊት የእጓለ ገብረ ዮሐንስ ‘የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ’ ለመጀመሪያ ጊዜ ካነበብኹ በኋላ ጸሐፊውን ከዚያ በፊት አለማወቄ ገርሞኝ እንደነበር አስታውሳለኹ ። ማን ናቸው ? እንዴት እስከዛሬ ድረስ ስለእርሳቸው ሳልሰማ ቀረኹ ? ለምን ? ይኼ በ1956 ዓ.ም. የታተመ የሬድዮ ንግግር ከኾነ መጽሐፍ ለመጻፍ ብለው ተነሥተው ቢጽፉ ኖሮ ምን ሊጽፉ ነበረ ? ወዘተ. የሚሉ ጥያቄዎች ጭንቅላቴ ውስጥ ተመላልሰዋል ።[1] በኋላ ፈላስፋው ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ፣ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተማሪና መምህር እንደነበሩ ስሰማ በመጽሐፉ ውስጥ ያየሁት የሐሳብ ጥልቀት በዘመኑ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ልሒቃን ዘንድ የነበረው ተዋሥኦ ሊደርስ ይንጠራራበት የነበረውን ልክ የጠቆመኝ መሰለኝ ። ከዚያ በኋላ ያ የተዋሥኦ ልሕቀት የት ገባ ? እንዴት ድርቅና የተጫነው ተዋሥኦ ዋጠው ? እንዴት ኦርቶዶክሳዊነትን ከአመክንዮ የተፋታ እና አመክንዮን የሚፈራ ጭፍን እምነት የሚያስመስሉ የፎክሎር ሰባኪዎች ተፈለፈሉብን ?  የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህን ለመኾን የሚጠየቀው መስፈርት ስለምን ድፍረት የለበሰ አላዋቂነት መሰለ ? በሚዲያ ላይ ሲናገሩ በአላዋቂነታቸው አንገታችንን የማያስደፉን ካህናት ስለምን ቁጥራቸው አልበረክት አለን ? ኦርቶዶክሳዊነት ችግርን እና ጭንቀትን ለማረሳሳት የተጠመቀ ዕፀ-ዝንጋዔ (‘opium of the masses’) እስኪመስል ድረስ በኦርቶዶክሳዊነት ስም የገነነው ተዋሥኦ ለምን አላዋቂነት ተጫነው ? ቤተ ክርስቲያን ሲባል ከስሜታዊ ሙጥኝታ (sentimental attachment) ባለፈ ለሰው ልጅ ህልውናዊ ጥያቄ የተሰጠ ከሞት ፍርኃት

Read More »
Emmaus Posts
በርናባስ ሽፈራው

ክፍል ፭ ፡ ወደ ርስታችን ያልተመለስንበት ኢዮቤልዩ

ሩሲያዊው ደራሲ ፌዮዶር ዶስቶየቭስኪ በ1860ዎቹ አውሮፓን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲጎበኝ የታዘበውን በዘገበበት ማስታወሻው የለንደን ድሆች ቅዳሜ ማታን እንዴት ባለ መንገድ እንደሚያሳልፉ ይነግረናል ። በቅድሚያ ሌሊቱን በሙሉ ወንዶች ብቻ ሳይሆኑ ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው ጭምር ደስታ ፈጽሞ በተለየው ፣ ድብርት በተጫነው መንፈስ አኳዃን ሲበሉ እና ሲጠጡ ፣ ከሕይወታቸው መራራነት ለማምለጥ ፣ ራሳቸውን ፍጹም ለማደንዘዝ በሙሉ ጥምብዝ እስኪሉ እንደሚሰክሩ መስማቱን ይዘግባል ። ሳምንቱን ሙሉ ሠርተው የቋጠሯትን ገንዘብ ቅዳሜ ሌሊት እንዲህ ይበትኗታል ። አስከትሎም እንዲህ ባለው አንድ ምሽት እሱ ራሱ በመንደራቸው ውስጥ ሲያልፍ የታዘበውን እና የተሰማውን እንደሚከተለው ይመሰክራል ። “One such night – it was getting on for two o’clock in the morning – I lost my way and for a long time trudged the streets in the midst of a vast crowd of gloomy people, asking my way almost by gestures, because I do not know a word of English. I found my way, but the impression of what I had seen tormented me for three days afterwards. The populace is much the same anywhere, but there all was so vast, so vivid that you almost physically felt things which up till then you had only imagined. In London, you no longer see the populace. Instead, you see a loss of sensibility, systematic, resigned and

Read More »
Emmaus Posts
በርናባስ ሽፈራው

ብያኔን አሳልፎ ያለመስጠት ግዴታ

ከሁለት ሳምንታት በፊት ‘ከጥያቄዎቹ በላይ አደገኛ የሆኑት መልሶች’ በሚል ርእስ አንድ ጽሑፍ አቅርበን ነበር ። ጽሑፉ በዋናነት ማሳነስ (reductionism) የተባለውን ፅንሰ ሐሳብ የሚያነሣ እና የሚተች ነው ። በዚህ ጽሑፋችን ውስጥ መምህር ያረጋል አበጋዝ በቅርቡ ‘ወደ ላይ አያዳልጣችሁ’ በሚል ርእስ ገዳማዊ ሕይወትን ከዘነበ ወላ ዘለፋ ለመከላከል ጽፎ ያጋራውን ጽሑፍ ተችተናል ። ርእሱን በዚህ ጊዜ ጉዳይ ያደረግነውም በዋናነት በምምህር ያረጋል ጽሑፍ ምክንያት ነው ። በተለይ ጽሑፉ ሰፊ ተነባቢነት እና ተቀባይነት ያገኘ እንደ መሆኑ በውስጡ ያየነውን የማሳነስ ዝንባሌ መተቸቱ ጠቃሚ ይሆናል ብለን አመንን ። ነገር ግን የመምህር ያረጋል ጽሑፍ መነሻ ቢሆነንም በይበልጥ ፅንሰ ሐሳቡ ላይ ለማተኮር ነው የሞከርነው – ዓላማችን ነገሩ ላይ ተዋሥኦ እንዲጀመርና የተሻለ መረዳት እንዲፈጠር ማድረግ ስለሆነ ። መምህር ያረጋልም ጽሑፉን ተመልክቶ ምላሽ ሰጥቶናል ። ምላሽ በመስጠቱ ደስ ብሎናል ። በምላሹ ግን አልተደሰትንም ። አለመደሰታችን እኛ በእርሱ ጽሑፍ ላይ ያቀረብነውን ትችት ባለመቀበሉ አይደለም ። ይልቁንም የተሰጠው ምላሽ ከእኛ ትችት ጋር እምብዛም የተያያዘ ባለመሆኑ እንጂ ። ከነገሩ ጋር የማይገጥሙ ምሳሌዎች ቀርበዋል ። ያቀረብነው ሂስ በተሳሳተ መንገድ ተተርጉሟል ። በጽሑፋችን በስም ጠርተን ያራቅነው እና ያነወርነው ሐሳብ የእኛ አቋም ተደርጎ ተገልጧል ። “ለቤተ ክርስቲያን ከልባችን ከመጨነቅና ከመቅናት” ተነሥተን “ያልተባለውን ለማስመሰል በመድከማችን” ተወቅሰናል ፤ ዕጣችን ሆኖ “ሳንነቅፍ መጻፍ አልቻልንምና” ። እነዚህ ሁሉ ነገሮች መልስ እና እርማት የሚሹ ሆነው አግኝተናቸዋል ። አንድም ለእኛም ሆነ ለመምህር ያረጋል

Read More »